1. ፍጥረት

1. ፍጥረት — illustration 1

ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው እግዚአብሔር የሁሉም ነገር ጀማሪ መሆኑን ነው። ስለሆነም እግዚአብሔር ዓለምንና በውስጧ የሚገኙትን ነገሮች በስድስት ቀናት ፈጠረ። እግዚአብሔር ምድርን ከፈጠረ በኋላ ምድር ጨለማና ባዶ ነበረች፤ በውስጧምንም ነገር ገና አልተፈጠረም ነበር። ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር መንፈስ በውሆች ላይሰፍፎ ነበር።

1. ፍጥረት — illustration 2

ከዚያም እግዚአብሔር “ብርሃን ይሁን” አለ ብርሃንም ሆነ። እግዚአብሔርም ብርሃኑ መልካም እንደሆነ አይቶ “ቀን” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም ቀኑን ከጨለማ ለይቶ ጨለማውን ሌሊት ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም በመጀመሪያው ቀን ብርሃንን ፈጠረ።

1. ፍጥረት — illustration 3

በሁለተኛው ቀን እግዚአብሔር ከምድር በላይ ያለውን ጠፈር ፈጠረ። ስለሆነም እግዚአብሔር ውሃን ከጠፈር ለየ።

1. ፍጥረት — illustration 4

በሦስተኛው ቀን እግዚአብሔር ውሃውን ከደረቁ መሬት እንዲለይ አደረገ። እግዚአብሔርም ደረቁን መሬት “ምድር” ውሃውንም “ባሕር” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

1. ፍጥረት — illustration 5

ከዚያም እግዚአብሔር ምድር ሁሉንም ዓይነት ዛፎችንና ተክሎችን ታብቅል አለ፣ እንዲሁም ሆነ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

1. ፍጥረት — illustration 6

በአራተኛው የፍጥረት ቀን እግዚአብሔር ፀሐይን፣ ጨረቃንና ክዋክብትን ፈጠረ። እግዚአብሔር ቀንና ሌሊትንም ወቅቶችንና ዓመታትንም እንዲለዩ አደረገ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

1. ፍጥረት — illustration 7

በአምስተኛው ቀን እግዚአብሔር በውሃ ውስጥ የሚኖሩትንና ወፎችን ሁሉ ፈጠረ። እግዚአብሔር ያ መልካም እንደ ሆነ አየ የተፈጠሩትንም ባረካቸው።

1. ፍጥረት — illustration 8

በስድስተኛውም ቀን፣ እግዚአብሔር “በምድር ላይ ሁሉም ዓይነት እንስሳት ይሁኑ” አለ። እግዚአብሔር እንዳለውም ሆነ። አንዳንዶቹ የእርሻ ከብቶች፣ አንዳንዶቹ በምድር የሚሳቡ፣ አንዳንዶቹ የዱር እንስሳት ነበሩ። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ።

1. ፍጥረት — illustration 9

እግዚአብሔር “ሰዎችን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር እነርሱም በምድር ሁሉና በእንስሳት ሁሉ ላይ ሥልጣን ይኑራቸው” አለ።

1. ፍጥረት — illustration 10

ስለዚህ እግዚአብሔር ከምድር አፈር ወስዶ ሰው አድርጐ አበጀና የሕይወትን እስትንፋስ ሰጠው። የዚህም ሰው ስም አዳም ተባለ። እግዚአብሔር አዳም በሚኖርበት ስፍራ አትክልት ተከለና እንዲያለማው እዚያው አስቀመጠው።

1. ፍጥረት — illustration 11

በአትክልቱም መካከል እግዚአብሔር ሁለት የተለዩ ዛፎችን ተከለ፤ የሕይወት ዛፍና መልካምና ክፉን መለየት የሚያስችል የእውቀት ዛፎች ነበሩ። እግዚአብሔርም አዳምን በአትክልቱ ስፍራ ካለው መልካምንና ክፉን መለየት ከሚያስችለው የእውቀት ዛፍ በቀር በአትክልቱ ውስጥ ካለው ከየትኛውም ዛፍ መብላት እንደሚችል ተናገረው። ነገር ግን ክፉውንና መልካሙን መለየት ከሚያስችለው ዛፍ ቢበላ እንደሚሞት ተናግሮት ነበር።

1. ፍጥረት — illustration 12

እግዚአብሔር ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም እንዳይደለ ተናገረው። ከእንስሳቱ አንዳቸውም የአዳም ረዳት ሊሆኑ አልቻሉም።

1. ፍጥረት — illustration 13

እግዚአብሔርም በአዳም ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣለበት አንቀላፍቶም ሳለ ከጐድኑ አንዲት አጥንት ወስዶ ሴት አድርጎ ሠራትና ወደ አዳም አመጣት።

1. ፍጥረት — illustration 14

አዳምም ባያት ጊዜ እንዲህ አለ፤ “ይህች እኔኑ ትመስላለች ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል።

1. ፍጥረት — illustration 15

እግዚአብሔር ወንድና ሴትን በራሱ መልክ ፈጠረ። እግዚአብሔርም ባረካቸው፤ አላቸውም “ብዙ ልጆችና የልጅ ልጆችም ይኑሩአችሁ ምድርንም ሙሉአት” እግዚአብሔርም የሠራው ነገር በጣም ጥሩ እንደ ነበር አየ። በሁሉም ነገር ተደሰተ ይህ ሁሉ በስድስት ቀን ሆነ።

1. ፍጥረት — illustration 16

በሰባተኛውም ቀን እግዚአብሔር የመፍጠር ሥራውን ፈጸመ። ስለዚህ እግዚአብሔር ሲሠራው ከነበረው ሥራ ሁሉ አረፈ፤ ሰባተኛውንም ቀን ባረከው ቀደሰውም። ምክንያቱም በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ አርፏልና። እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን በውስጧም የሚገኙትን በፈጠረ ጊዜ የተከናወኑት በዚህ ሁኔታ ነበር።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘፍጥረት 1-2።

Read in the reader

Free to use, adapt, and share under an open license (CC BY-SA 4.0).